የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መምሪያ

ለዚህ ሳምንት ጥናት፡ መዝ 18፡3–18፤ መዝ 41:1–3፤ ዘዳ 15፡7–11፤ መዝ 82፤ መዝ 96፡
6–10፤ መዝ 99፡1–4፤ ሮሜ 8፡34 ያንብቡ።
የመታሰቢያ ጥቅስ፡- ስለ ድሆች ግፍና ስለ ችግረኞች ጩኸት አሁን
እነሣለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር። መድኃኒትን አደርጋለሁ፥ በላዩም
እገልጣለሁ (መዝ 12፡5)
ክፋት፣ ኢ-ፍትሃዊነት እና ጭቆና የተንሰራፋበት የኛ ዘመን ብቻ አይደለም።
መዝሙረኞቹም ተመሳሳይ ዓይነት ችግር በነበረበት ዘመን ኖረዋል። ሁኔታዎቹ
ምንም ቢሆኑም፣ መዝሙራቱ በአለማችን እና በመዝሙረኛው ላይ የሚደርሰውን
ግፍ እና ጭቆና የሚቃወሙ የእግዚአብሔር ተቃውሞዎች ናቸው።
አዎን፣ ጌታ ታጋሽ እና በታላቅ ትዕግሥቱ ለቁጣ የዘገየ ነው፣ ማንም እንዲጠፋ
ስለማይፈልግ ሁሉም ንስሐ እንዲገቡ እና መንገዳቸውን እንዲለውጡ ይፈልጋል (2ጴጥ
3፡9-15)። ምንም እንኳን እግዚአብሔር ጣልቃ የሚገባበት ትክክለኛ ጊዜ ሁልጊዜ ሰው
ከሚጠብቀው ጋር ባይጣጣምም፣ የእግዚአብሔር የፍርድ ቀን እየመጣ ነው (መዝ
96፡13፣ መዝ 98፡9)። ያ ቀን እስኪመጣ ድረስ በእርሱ እና በተስፋዎቹ ብቻ መታመን
ያስፈልገናል። ዙፋኑ በጽድቅና በፍትሕ ላይ የተመሰረተው ፈጣሪ ብቻ ለዓለም (መዝ 89፡
14፣ መዝ 97፡2)፣ በሉዓላዊ ፍርዱ መረጋጋትንና ብልጽግናን ይሰጣል። የተጨቆኑት መዳን
እና የክፉዎች መጥፋት የመለኮታዊ ፍርድን ሁለት ገጽታዎች ያጠቃልላል (መዝ 7፡6-17)።
ቃል የተገባልንም ይህ ነው፣ በእርግጥም አንድ ቀን የሚሆነው ይህ ነው—ነገር ግን
መዝሙረኛው አጽንዖት የሰጠው ነጥብ በእግዚአብሔር ጊዜ እንጂ በእኛ ጊዜ እንደማይሆን
ነው።
ለየካቲት 2 ሰንበት ለመዘጋጀት የዚህን ሳምንት ትምህርት ያጥኑ
መዝ 18:3–18፤ መዝ 76:3–9፣12፤ እና መዝ 144:5-7ን ያንብቡ። በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ጌታ እንዴት ተገለጠ? እነዚህ ምስሎች አምላክ ሕዝቡን ለማዳን ስላለው ዝግጁነት ምን ያስተላልፋሉ?
እነዚህ መዝሙሮች ሕዝቡን በሚያስፈራሩ ክፉ ኃይሎች ላይ ስላለው አስፈሪ
ኃይል ጌታን ያወድሳሉ። እግዚአብሔርን በለግርማው ጦረኛና ፈራጅ አድርገው
ይስሉታል። እግዚአብሔርን እንደ ተዋጊ አድርጎ የሚያቀርበው ምስል በመዝሙሮች
ውስጥ ተደጋግሞ አለ፤ ይህም እግዚአብሔር ለህዝቡ ጩኸት እና ስቃይ የሚሰጠውን
ምላሽ ክብደት እና አጣዳፊነት ያጎላል።
“እግዚአብሔር ከሰማይ አንጐደጐደ፥ ልዑልም ቃሉን ተናገረ፥ የበረዶ ድንጋይና
የእሳት ፍም ፍላጻዎቹን ሰደደ፥ ጠላቱንም በተነ፥ መብረቅንም አበዛ፥ አሸነፋቸውም።
ባሕር ታየ፥ የዓለም መሠረቶች ተገለጡ። አቤቱ፥ ከተግሣጽህ፥ ከአፍንጫህም እስትንፋስ
የተነሣ ተገለጠ” (መዝ 18፡13-15)።
የእግዚአብሔር ድርጊት ታላቅ ቁርጠኝነት እና የድርጊቱ መጠን እግዚአብሔር ለተጎዱት
ሰዎች ስላለው ታላቅ ጥንቃቄ እና ርኅራኄ ያለውን ጥርጣሬ ወይም ክፋትን ስለማሸነፉ ያለብንን
ጥርጣሬ ማስወገድ አለበት። እርሱ እንዲያደርግልን ዝም ብለን መጠበቅ አለብን።
ውሎ አድሮ፣ እንደ ዳዊት ያሉ የአምላክ ሕዝቦች በጦርነት ውስጥ በተሳተፉበት
ጊዜም እንኳ መዳን በሰው ኃይል አልተገኘም። ንጉሥ ዳዊት ከአምላክ ሕዝቦች ጠላቶች ጋር
ባደረገው በርካታ ውጊያዎች ሁሉንም ድሎች ያስመዘገበው አምላክ ብቻ እንደሆነ በመግለጽ
አወድሶታል። ዳዊት ለብዙ ስኬቶቹ እና ድሎቹ ምስጋናውን መቀበል ቀላል ይሆን ነበር፣
ነገር ግን ይህ የእርሱ አሳብ አልነበረም። የኃይሉ ምንጭ ከየት እንደመጣ ያውቅ ነበር።
ምንም እንኳን ዳዊት እግዚአብሔር እጆቹን ለጦርነት እንደሚያሠለጥን ቢናገርም
(መዝ 18፡34) በመዝሙራት ውስጥ ግን የትም ቢሆን በጦርነት ችሎታው አልተደገፈም።
ይልቁንም እግዚአብሔር ስለ ዳዊት ተዋግቶ አዳነው (መዝ 18:47፡ 48)። በመዝሙሩ
የጎልማሶች ሰንበት ትምህርት መምሪያ መጽሐፈ መዝሙረ ዳዊት
ውስጥ፣ የተዋጣለት ተዋጊ በመባል የሚታወቀው ንጉሥ ዳዊት፣ የተዋጣለት ሙዚቀኛ
በመሆን ሚናውን ወስዶ ጌታን የሕዝቡ ብቸኛ አዳኝ እና ደጋፊ አድርጎ አወድሶታል
(መዝ 144፡10-15)። ለእግዚአብሔር የሚያቀርበው ምስጋና እና ጸሎት ከየትኛውም የጦር
መሣሪያ የበለጠ ኃይለኛ የዳዊት የጥንካሬ ምንጮች ናቸው። መታመንና መመለክ ያለበት
እግዚአብሔር ብቻ ነው።
በህይወትዎ ውስጥ ምንም አይነት ስጦታዎችና ችሎታዎች እና ስኬት ያግኙ፤ የሁሉም
ምንጭ ማን እንደሆነ ሁል ጊዜ ማስታወስ ያለብዎት ለምንድን ነው? ያንን ምንጭ ከረሱ
ምን አደጋ ያጋጥምዎታል?
መዝ 9:18፤ መዝ 12:5፤ መዝ 40:17፤ መዝሙር 113:7፤ መዝ 146:6-10 እና መዝ 41:1-3 ያንብቡ። ዛሬም ቢሆን ለእኛ መልእክቱ ምንድን ነው?
አምላክ ለድሆች፣ ለችግረኞች፣ ለተጨቆኑ፣ አባት ለሌላቸው፣ ለመበለቶች፣
ሚስት ለሞተባቸው እና እንግዶችን ጨምሮ ለተለያዩ ተጋላጭ ለሆኑ ወገኖች ፍትሕ ልዩ
እንክብካቤ እና አሳቢነት አሳይቷል። በዚህ ነጥብ ላይ መዝሙራት፣ እንደ ሕግና ነቢያት፣
ግልጽ ናቸው (ዘጸ 22፡21–27፤ ኢሳ 3፡13-15)።
ብዙ መዝሙራት “ድሆችና ችግረኞች” የሚለውን አገላለጽ የሚጠቀሙ ሲሆን
የተጨቆኑትን የሚለውን በብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ቃላት ብቻ ከመወከል ይቆጠባሉ። ይህ
የሚያሳየው እግዚአብሔር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሰው ልጆች ያለውን ሁለንተናዊ እንክብካቤ
ነው። “ድሆች እና ችግረኞች” የሚለው አገላለጽ ቁሳዊ ድህነትን ብቻ ሳይሆን ሁለንተናዊ
ተጋላጭነትን እና እረዳት አልባነትንም ያመለክታል። አገላለጹ የእግዚአብሔርን ርኅራኄ የሚስብ
ነው፤ ተጎጂው ብቻውን እንደሆነ እና ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ ረዳት እንደሌለው ይገልጻል።
“ድሆች እና ችግረኞች” የሚለው ሥዕላዊ መግለጫ በቁሳዊ ድህነት ላይ
ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ተጋላጭነትንና ረዳት የለሽነትንም ያመለክታል። መግለጫው
ለእግዚአብሔር ርኅራኄ ተማጽኖውን በማቅረብ በሠቆቃ ላይ ያለው ሰው ብቻውን
እንደሆነ እና ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ ማንም እንደሌለው የሚገልጽ ሀሳብ ያስተላልፋል።
“ድሆች እና ችግረኞች” የሚለው መግለጫ አንድ ሰው በእግዚአብሔር ላይ ያለውን ሙሉ
ጥገኝነትን በማመን እና በራስ የመተማመንን ምልክት በመተው ለእግዚአብሔር ያለውን
ቅንነት፣ እውነተኝነት እና ፍቅር ያመለክታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የተቸገሩትን መንከባከብ (መዝ 41፡1-3) ሰዎች ለእግዚአብሔር
ያላቸውን ታማኝነት ያሳያል። በተለይ በተጎጂዎች ላይ የሚደረጉ ክፋቶች በመጽሐፍ
ቅዱሳዊ ባህል ውስጥ አስከፊ ኃጢአቶች ነበሩ (ዘዳ 15፡7–11)። መዝሙራት ታማኝ ሰዎች
በእያንዳንዱ ጭቆና ላይ ድምፃቸውን እንዲያሰሙ አነሳስተዋል። መዝሙራት አንድ ሰው
ጠፊ በሆነው የሰው ሃብት ላይ መተማመንን እንደ የመጨረሻው የጥበብ እና የደኅንነት
ምንጭ አድርጎ መተማመን ከንቱነት መሆኑን ያሰምርበታል። የአምላክ ሕዝቦች፣ በተለይም
ከእግዚአብሔር መንገዶች በሚለዩበት ጊዜ፣ ለመዳን በሰብዓዊ መሪዎችና ተቋማት ላይ
እምነት እንዲጥሉ የሚመጣባቸውን የመጨረሻውን ፈተና መቋቋም አለባቸው።
ጌታችን በጸጋው በእርሱ ድህነት ብዙዎች ባለ ጠጎች እንዲሆኑ ራሱ ድሃ በመሆን
ከድሆች ጋር ተዋወቀ (2ቆሮ 8፡9)። የክርስቶስ ባለጠግነት ኃጢአት ከሚያመጣቸው
ጭቆናዎች ሁሉ ነፃ መውጣትን ያጠቃልላል፣ በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ የዘላለም
ሕይወት እንደሚኖረን ቃል ገብቷል (ራዕ 21፡4)። ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ መለኮታዊ ፈራጅ
የመዝሙራትን ተስፋዎች ይፈጽማል፣ ጭቁኖች ለደረሰባቸው በደል ሁሉ እና እንዲሁም
ለእነርሱ ሊደረግላቸው ሲገባ ችላ ስለተባሉ ተግባራት ይፈርዳል (ማቴ 25፡31-46)።
በመካከላችን ላሉ “ድሆችና ችግረኞች” ምን ያህል እናስባለን፤ ምን ያህልስ መልካም
እናደርግላቸዋለን?
የእስራኤል መሪዎች በእስራኤል ፍትህን እንዲያሰፍኑ ጌታ ስልጣን ሰጥቷቸዋል (መዝ 72፡1-7፤ 12-14)። የእስራኤል ነገሥታት ሥልጣናቸውን በአምላክ ፈቃድ መሠረት መጠቀም ነበረባቸው። የመሪዎቹ ማዕከላዊ ጉዳይ በምድሪቱ ላይ ሰላምና ፍትህን ማረጋገጥ እና በማህበራዊ ጉዳት ውስጥ ያሉትን መንከባከብ መሆን አለበት። ያኔ ብቻ ነው ምድሪቱና መላው ህዝብ የሚበለፅገው። የንጉሱ ዙፋን የሚጸናው በሰው ኃይል ሳይሆን ለእግዚአብሔር ባለው ታማኝነት ነው። የጎልማሶች ሰንበት ትምህርት መምሪያ መጽሐፈ መዝሙረ ዳዊት መዝሙር 82ን ያንብቡ። መሪዎች ፍትህን ሲያጣምሙ እና እንዲጠብቁ የተሰጣቸውን ህዝብ ሲጨቁኑ ምን ይሆናል?
በመዝሙር 82 ላይ፣ እግዚአብሔር በተበላሹ የእስራኤል ፈራጆች ላይ ፍርዱን
ተናገረ። “አማልክት” ( መዝ 82:1፣ 6) አረማዊ አማልክትም ሆኑ መላእክት አይደሉም፤
ምክንያቱም ለአምላክ ሕዝቦች ፍትሕ የማድረግ ኃላፊነት ፈጽሞ ስላልተጣለባቸው ፍትሕን
ባለማሟላታቸው ሊፈረድባቸው አይችልም። በመዝ 82፡2-4 የተዘረዘሩት መጠይቆች
“አማልክት”ን እንደ እስራኤል መሪዎች በመግለጽ የኦሪትን ህግጋት ያስተጋባሉ (ዘዳ 1፡16-
18፤ ዘዳ 16፡18-20፤ ዮሐ 10፡33–35)። እግዚአብሔር “የሰው ልጆችን” በጽድቅ ይፈርዱ
ወይም አይፈርዱ እንደሆነ ይመለከታቸዋል፤ ዓመፀኛ ሆነው ስለተገኙ ቅጣታቸውም
ተገልጾአል። አለቆቹ ያለ እውቀት በጨለማ ይርመሰመሳሉ (መዝ 82፡5)፣ ምክንያቱም
የእግዚአብሔርን ህግ ብርሃን ትተዋል (መዝ 119፡105)።
ቅዱሳት መጻሕፍት ጌታ ብቻውን አምላክ ነው የሚለውን አመለካከት ያለማወላወል
ይደግፋሉ። እግዚአብሔር የእርሱ ተወካዮች ሆነው ከተሾሙ ሰብዓዊ መሪዎች ጋር ዓለምን
በማስተዳደር ይጋራል (ሮሜ 13፡1)። ይሁን እንጂ እነዚህ ሰብዓዊ ተወካዮች በታሪክም ሆነ
በአሁኑ ጊዜ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ምን ያህል ጊዜ አዛብተውታል? መዝሙር 82 ራሳቸውን
ከሌሎች ሰዎች በላይ “አማልክት” እንደሆኑ የሚያምኑ የአንዳንድ መሪዎችን ክህደት በመሳለቅ
ያጋልጣል። አምላክ ለእስራኤላውያን መሪዎች ‘የልዑል ልጆች’ ተብለው ተጠርተው እርሱን
እንዲወክሉ ሥልጣንና ልዩ መብት ቢሰጣቸውም እግዚአብሔር ክፉ መሪዎችን ትቶአቸዋል።
እግዚአብሔር ሟች እንደሆኑ እና እንደ ሁሉም ሰዎች በተመሳሳይ የሞራል ህግጋት እንደሚገዙ
ያሳስባቸዋል። ማንም ከእግዚአብሔር ሕግ በላይ አይደለም (መዝ 82፡6-8)።
እግዚአብሔር በዓለም ሁሉ ላይ ይፈርዳል፤ የእግዚአብሔር ሕዝብም
ለእግዚአብሔር መልስ ይሰጣሉ። መሪዎቹም ሆኑ ህዝቡ የመለኮታዊውን ዳኛ ምሳሌ
በመከተል የመጨረሻ ተስፋቸውን በእርሱ ላይ ማድረግ አለባቸው።
በሌሎች ላይ ምን አይነት ስልጣን ነው ያለዎት? ያንን ስልጣን ምን ያህል ፍትሃዊ እና
ትክክለኛ በሆነ መንገድ እየተጠቀሙበት ነው? ልብ ይበሉ።
መዝ 58:6–8፤ መዝ 69:22-28፤ መዝ 83:9-17፤ መዝ 94:1፣ 2፤ እና መዝ 137:7-9ን ያንብቡ። እነዚህ መዝሙሮች ምን ዓይነት ስሜቶችን ያስተላልፋሉ? በእነዚህ መዝሙሮች ውስጥ የፍርድ ወኪል ማን ነው?
አንዳንድ መዝሙሮች እግዚአብሔርን፣ሕዝቡን ወይም መዝሙረኞቹን ለመጉዳት
ያሰቡትን ወይም ቀደም ሲል በሕዝቡ ላይ ጉዳት ያደረሱ ግለሰቦችንና ሕዝቦችን እንዲበቀል
ተማጽኖ ያቀርባሉ። እነዚህ መዝሙራት በጭካኔ ንግግራቸው ከመጽሐፍ ቅዱሳዊው
ጠላትን ከመውደድ ፍቅር መርህ ጋር የሚጣረሱ ሊመስሉ ይችላሉ (ማቴ 5፡44)።
ሆኖም መዝሙረኛው ጭቆና ሲደርስበት የተሰማው ቁጣ ተገቢ ነው። ይህን
ማለት መዝሙረኞቹ ከብዙ ሰዎች ይልቅ ትክክልና ስህተት የሆነውን ነገር በቁም ነገር
ይመለከቱ ነበር ማለት ነው። ለራሱ ብቻ ሳይሆን በዓለም በሌሎችም ላይ ስለሚደረገው
ክፋት በጣም ያስባል።
ይሁን እንጂ መዝሙረኛው የትም ቦታ ራሱን የበቀል ወኪል አድርጎ አላቀረበም።
ይልቁንም ቅጣቱን በእግዚአብሔር እጅ ላይ ብቻ ይተወዋል። መዝሙራቱ የመለኮታዊውን
የቃል ኪዳን እርግማን በማነሳሳት (ዘዳ 27፡9-16) እግዚአብሔር እንደገባው ቃል እንዲሰራ
ተማጸኑ።
መዝሙራቱ ስለሚመጣው የእግዚአብሔር ፍርድ ትንቢታዊ አዋጆች ናቸው
እንጂ የመዝሙረኛው ጸሎቶች ብቻ አይደሉም። በነቢያት እንደተነገረው ሁሉ መዝሙር
137 በባቢሎን ላይ የተናገረውን የመለኮታዊ ፍርድ አዋጅ ያንጸባርቃል። ባቢሎናውያን
በሌሎች ሕዝቦች ላይ ያደረሱት ጥፋት ወደ ራሳቸው ይመለሳል። መዝሙራት ክፋት
ለዘላለም ሳይቀጣ እንደማይታለፍ አድርገው መለኮታዊ ማስጠንቀቂያዎችን ያስተላልፋሉ።
የእግዚአብሔር ቅጣት የሚለካው በፍትህ እና በጸጋ ነው። የእግዚአብሔር
ልጆች ለሚበድሏቸው እንዲጸልዩ እና እንዲያውም እንደሚለወጡ ተስፋ እንዲያደርጉ
ተጠርተዋል (መዝ 83፡18፣ ኤር 29፡7)።
የጎልማሶች ሰንበት ትምህርት መምሪያ መጽሐፈ መዝሙረ ዳዊት
ነገር ግን፣ እነዚህን መዝሙራት ጠላቶችን ስለ መውደድ ከተጻፉት ከመጽሐፍ
ቅዱሳዊ ደንቦች ጋር ለማስማማት ስንል፣ በውስጣቸው የተገለጸውን አሳዛኝ ተሞክሮ
እንዳንቀንስ መጠንቀቅ አለብን። እግዚአብሔር የልጆቹን ስቃይ እውቅና ሲሰጥ
“የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው” ሲል አረጋግጦላቸዋል (መዝ 116፡15)።
መለኮታዊ ፍርድ የእግዚአብሔር ሕዝብ በክፉ ሁሉ ላይ ድምፃቸውን እንዲያሰሙ እና
የእግዚአብሔርን መንግሥት በሙላቱ እንዲመጣ እንዲፈልጉ ያስገድዳቸዋል። መዝሙራት
መከራ ለደረሰባቸው ሰዎች እግዚአብሔር ስቃያቸውን እንደሚያውቅና አንድ ቀን ፍትህ
እንደሚመጣ እንዲያውቁ ድምፅን ይሰጣሉ።
አንዳንድ ጊዜ በእነርሱ ወይም በሚወዷቸው ሰዎች ላይ አስከፊ ግፍ በፈጸሙት ላይ
የበቀል ሀሳብ ወይም ምኞት የሌለው ማነው? እነዚህ መዝሙራት እንዲህ ያለውን ስሜት
በተገቢው መንገድ እንዲይዙ ሊረዱዎ የሚችሉት እንዴት ነው?
መዝ 96:6–10፤ መዝ 99:1-4፤ እና መዝ 132:7–9፤ 13–18ን ያንብቡ።
የአምላክ ፍርድ የሚፈጸመው የት ነው? መልሱስ ለእኛ ምን አንደምታ አለው? መቅደሱ
እግዚአብሔር ክፋትን እንዴት እንደሚይዝ እንድንረዳ የሚረዳን እንዴት ነው?
የጌታ ፍርድ ከመቅደሱ ጋር በቅርበት የተቆራኘ ነው። መቅደሱ መዝሙረኛው ስለ
ክፋት ችግር ያለው መረዳት የተለወጠበት ቦታ ነበር (መዝ 73፡17-20)። መቅደሱ በኡሪም
በሚታየው መሰረት ፍርድ የሚሰጥበት ቦታ(ዘኁ 27፡21) እና በሊቀ ካህናቱ የፍርድ ጥሩር
እንደተገለጸው የመለኮታዊ ፍርድ ቦታ ሆኖ የተሰየመ ነው (ዘጸ 28፡15፣ 28–30)። በዚህም
መሰረት፣ ብዙ መዝሙራት እግዚአብሔርን በመቅደሱ ውስጥ በዙፋኑ ላይ ዓለምን ስለ
ኃጢአቱና ስለ ክፋቱ ለመፍረድ እንደተዘጋጀ ይገልፁታል።
በመቅደስ ውስጥ የመዳን እቅድ ተገልጦ ነበር። በአህዛብ አምልኮ ኃጢአት
በዋነኛነት የተስተዋለው በአስማት የአምልኮ ሥርዓቶች እንደሚወገድ እንደ አካላዊ ጉድፍ
ነበር። ከዚህ በተቃራኒ መጽሐፍ ቅዱስ ኃጢአት የአምላክን የሥነ ምግባር ሕግ መጣስ
እንደሆነ አድርጎ ይገልጸዋል። የእግዚአብሔር ቅድስና ፍትሕንና ጽድቅን ይወዳል ማለት
ነው። በተመሳሳይ፣ የእግዚአብሔር ሕዝብ ፍትሕንና ጽድቅን መከተል እና እግዚአብሔርን
በቅድስናው ማምለክ አለባቸው። ይህን ለማድረግ የቅድስናው መገለጫ የሆነውን
የእግዚአብሔርን ሕግ መጠበቅ አለባቸው።
ስለዚህ፣ መቅደሱ በእግዚአብሔር ዙፋን የስርየት መክደኛ እና “በጽድቅ
መስዋዕቶች” (ዘዳ 33:19፤ መዝ 4:5) እንደተገለፀው የኃጢአት ስርየት እና የጽድቅ መልሶ
ማቋቋም ቦታ ነው።
ሆኖም፣ “ይቅር የሚል አምላክ” ንስሐ በማይገቡ ሰዎች ክፉ ሥራ ላይ ይበቀላል
(መዝ 99፡8)። መቅደሱ የመለኮታዊ ፍርድ ቦታ የመሆኑ ተግባራዊ አንደምታ የሚታየው
የእግዚአብሔርን ቅድስና የማያቋርጥ ግንዛቤ እና በእግዚአብሔር የቃል ኪዳናዊ
መስፈርቶች መሰረት በጽድቅ የመኖር ፍላጎት ነው።
ጌታ በጽዮን የሚያደርገው ፍርድ ውጤቱ የጻድቃን ደህንነት እና የኃጥአን ሽንፈት
ነው (መዝ 132፡13–18)። መቅደሱ በተለይ በስርየት ቀን የጌታን እንደ ፈራጅ የመምጣት
አስደሳች ተስፋዎችን ያበረታታል። እንደዚሁም፣ መዝሙራት የመለኮታዊው ፈራጅ
(መዝ 96፡13፣ መዝ 98፡9) ማለትም ኢየሱስ ክርስቶስ በሰማያዊው መቅደስ የመምጣት
እርግጠኝነትን ያጠናክራሉ (ራዕ 11፡15-19)።
ሮሜ 8፡34ን ያንብቡ። ይህ ጥቅስ ክርስቶስ በሰማያዊው መቅደስ እያደረገ ያለው ነገር
ለህዝቡ የምስራች መሆኑን የሚያሳየን እንዴት ነው?
ከበረከት ተራራ የተወሰዱ ሀሳቦች ከሚል የኤለን ጂ ዋይት
መጽሐፍ “ብፁዓን ናችሁ” ከሚለው ርዕስ ገጽ 6–13፣ 29–35ን ያንብቡ።
መዝሙራት የሰው ልጅ ለፍትሕ መጓደል የሚያሳየውን ግድየለሽነት የሚቃወሙ
ናቸው፤ ክፋትን ለመቀበል እምቢ የማለት መገለጫ ናቸው። ለበቀል ባላቸው ፍላጎት
ሳይሆን የአምላክን ስም ለማክበር ባለ ቅንዓት ተነሳሽነት የተደረሱ ናቸው። ስለዚህ፣
ጻድቃን እግዚአብሔር ክፋትን ሲበቀል ሲያዩ ደስ ሊላቸው ይገባል፤ ምክንያቱም በዚህ
መንገድ የእግዚአብሔር ስም እና ፍትህ በዓለም ላይ እንደገና ይታደሳል (መዝ 58: 10፣ 11)።
መዝሙራት ሰዎች በክፉ ላይ ድምፃቸውን እንዲያሰሙ እና የእግዚአብሔርን መንግሥት
በሙላት እንዲመጣ እንዲጮኹ ያስገድዳቸዋል። በመዝሙራት ውስጥ፣ መለኮታዊ
ማጽናኛ እና መዳን ማረጋገጫ ተሰጥቶናል። ጌታ ይነሳል!
የጎልማሶች ሰንበት ትምህርት መምሪያ መጽሐፈ መዝሙረ ዳዊት
“ሰዎች ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ ደስ ይበላችሁ ሐሤትም አድርጉ” ብሎ
ሰሚዎቹን በጌታ ስም ወደ ተናገሩት ነቢያትና በመከራና በስቃይ ውስጥ በትዕግስት ወ
ደፀኑት አመለከተ (ያዕቆብ 5:10)። ከአዳም ልጆች የመጀመሪያው ክርስቲያን የሆነው አቤል
በሰማዕትነት ሞተ። ሄኖክ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፣ ዓለምም አላወቀውም።
ኖህን እንደ አክራሪ እና አስጠንቃቂ ተሳለቁበት። ‘ሌሎችም የተሻለ ትንሣኤ እንዲያገኙ’
ጭካኔ በተሞላበት ፌዝና ግርፋት ከዚህም በላይ እስራት ተፈትነዋል። ዕብራውያን 11:36፣
35።”—በተራራ ላይ የተሰበኩ ስብከቶች ገጽ 33።
1. በአለም ላይ ያለውን ክፋት በመገንዘቡ አንድ ሰው ጌታ በእርግጥ እየተቆጣጠረ ነው
በአለም ላይ ያለውን ክፋት በመገንዘቡ አንድ ሰው ጌታ በእርግጥ እየተቆጣጠረ ነው
ብሎ እንዲያስብ ሊያደርግ በሚያስችል ፈተና ውስጥ እንኳን የሚጸና የማይናወጥ
እምነትን እንዴት ማሳደግ ይችላል? ማለትም፣ በአምላክ ፍቅር፣ በጎነት እና ኃይል ላይ
ያለንን እምነት ለመጠበቅ ምን ላይ ማተኮር አለብን? መስቀሉ ስለ እግዚአብሔር እና
ስለ ባህሪው ምን ሊነግረን ይገባል?
2. በዓለም ላይ ላለው ፍትህ እንደ የመጨረሻ ጥበብና መፍትሔ አድርገን በሰዎች መንገድ
በዓለም ላይ ላለው ፍትህ እንደ የመጨረሻ ጥበብና መፍትሔ አድርገን በሰዎች መንገድ
(መሪዎች፣ ተቋማት እና ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎች) አለመታመን እና በእግዚአብሔር
ቃልና ፍርድ ላይ ብቻ መታመን አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
3. መቅደሱ የመለኮታዊ ፍርድ ቦታ ነው የሚለው የእውነት ተግባራዊ አንደምታ ምንድን
መቅደሱ የመለኮታዊ ፍርድ ቦታ ነው የሚለው የእውነት ተግባራዊ አንደምታ ምንድን
ነው?
4. የአንዳንድ መዝሙራትን ከባድ ቋንቋ እንዴት መረዳት እንችላለን? ይህ ቋንቋ
የአንዳንድ መዝሙራትን ከባድ ቋንቋ እንዴት መረዳት እንችላለን? ይህ ቋንቋ
ከጻፏቸው ሰዎች ሰብዓዊነት ጋር እንድንገናኝ የሚረዳን እንዴት ነው?