የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መምሪያ

ለዚህ ሳምንት ጥናት ያንብቡ፡ መዝ 27:14፤ ሮሜ 8:18–25፤ መዝ 131፤ ማቴ 18:3፤ መዝ 126፤ መዝ 92፤ ማር16:1-8፤ 2 ጴጥ 1፡19።
የመታሰቢያ ጥቅስ፡- እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤ በርታ፥ ልብህም
ይጽና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ። (መዝ 27:14)።
በዚህ የሩብ ዓመት ስናካሄድ ወደነበረው የመዝሙራት መጽሐፍ ጥናት የመጨረሻው
ሳምንት ላይ ደርሰናል። መንፈሳዊው ጉዞ በባለግርማው ፈጣሪ፣ ንጉስ እና ፈራጅ
ፊት የመደነቅ ልምምድ ውስጥ፤ በመለኮታዊ ነጻ የመውጣት እና ድነት ልምምድ
ውስጥ፤ በሀዘንና በእንባ ራስን አሳልፎ የመስጠት አጋጣሚዎች ልምምድ ውስጥ፤ እና
በግርማ በተሞላው በእግዚአብሔር መገኘት ዘላለማዊ ተስፋዎችና እግዚአብሔርን
ለዘላለም ማምለክን በተስፋ የመጠበቅ ልምምድ ውስጥ እንድናልፍ አድርጎናል። ነገር
ግን በጌታ መምጣት ተስፋ ስንኖር፣ ለእግዚአብሔር ያለን ናፍቆት የመጨረሻ ፍጻሜውን
እስከሚያገኝ ድረስ ጉዞው ይቀጥላል። ከመዝሙራት ልንወስደው የምንችለው የመጨረሻ
ቃል ካለ “እግዚአብሔርን ጠብቅ” የሚል መሆን አለበት።
ጌታን መጠበቅ ማለት አንድ ሰው ስራ ፈት እና ተስፋ የቆረጠ በመሆን ጊዜ
ማባከን ማለት ነው። ይልቁንም ጌታን መጠበቅ በእምነት እና በመታመን የተሞላና
እምነት በተግባር የሚገለጥበት ድርጊት ነው። ጌታን መጠበቅ የጨለማውን ምሽታችንን
በብሩህ ጥዋት ተስፋ ይለውጠዋል (መዝ 30፡5፣ መዝ 143፡8)። በአዲስ ተስፋ እና ሰላም
ልባችንን ያጸናዋል። ከጌታ የተልእኮ መስኮች የተትረፈረፈ የመከር ነዶን እንድናመጣ
የበለጠ እንድንሰራ ያነሳሳናል (መዝ 126፡6፣ ማቴ 9፡36–38)። ጌታን መጠባበቅ በፍፁም
አያሳፍረንም ነገር ግን በብዙ ያሸልመናል ምክንያቱም ጌታ ለተስፋ ቃሉ ሁሉ ታማኝ ነውና
(መዝ 37:7-11፣ 18፣ 34፤ መዝ 71:1፤ መዝ 119:137፣138)
ለመጋቢት 21 ሰንበት ለመዘጋጀት የዚህን ሳምንት ትምህርት አጥኑ።
መዝ 27:14፤ መዝ 37:7፣ 9፣ 34፤ መዝ 39:7፤ መዝ 40:1፤ መዝ 69:6፤ ገላትያ 5፡5፣ እና ሮሜ 8፡18–25ን ያንብቡ። እነዚህ ጥቅሶች የአምላክ ሕዝቦች ምን እንዲያደርጉ ይማጸናሉ?
ምናልባት በህይወት ውስጥ ካሉት ታላላቅ ጭንቀቶች አንዱ ከመጠበቅ የተነሳ
የሚመጣ ጭንቀት ነው። ማንም ብንሆን፣ የትም ብንኖር፣ በሕይወታችን ውስጥ ድርሻችን
ምንም ቢሆን፣ ሁላችንም አንዳንድ ጊዜ ነገሮችን የመጠበቅ ግዴታ አለብን። በአንድ ሱቅ
ውስጥ ወረፋ ከመጠበቅ ጀምሮ የሕክምና ምርመራ ውጤት ለመስማት መጠበቅ፣ ሁልጊዜ
ማድረግ የማንፈልገውን እንጠብቃለን፣ አይደል?
ታዲያ አምላክን ስለመጠበቅስ ምን ማለት ይቻላል? ጌታን መጠበቅ የሚለው
አስተሳሰብ በመዝሙራት ውስጥ ብቻ ሳይሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም በብዛት
ይገኛል። በዚህ ሁሉ ውስጥ የሚሰራው ፅናት የሚል ቃል ነው። ፅናት እግዚአብሔር
አይደርስልንም በሚል ስጋት ላለመሸነፍ ያለን ከፍተኛ ቁርጠኝነት ነው። የእግዚአብሔር
ታማኝ ልጅ ጌታን ይጠብቃል፣ እግዚአብሔር ታማኝ መሆኑን እና እርሱን የሚጠባበቁት
ደግሞ ያሉበትን ሁኔታ ለእርሱ ቢተዉት፣ ለጊዜው እነሱ በሚፈልጉት መንገድ እንኳን
ባይሆን ለጥቅማቸው እንደሚሰራ ይረዳሉ ።
ጌታን መጠበቅ ዝም ብሎ ከመቆየት በላይ ነው። በደረቅ ምድር ካለው ጽኑ
ጥም ጋር የሚነጻጸር የእግዚአብሔር ጥልቅ ናፍቆት ነው (መዝ 63፡1)። መዝሙረኛው
እግዚአብሔር የሚሰጠውን ብዙ በረከቶች ይጠብቃል፣ ነገር ግን ወደ አምላኩ ለመቅረብ
ያለው ጉጉት ከማንኛውም የሕይወት ፍላጎትና መሻት ይበልጣል።
ጳውሎስ ለሮሜ በጻፈው አስደናቂ ደብዳቤ ላይ እንደምናነበው፣ እግዚአብሔርና
መላው ፍጥረት የዓለምን መታደስ እና በዘመኑ ፍጻሜ የሚመጣውን የተባረከውን
የእግዚአብሔር እና የህዝቡን መሰባሰብ እየጠበቁ ናቸው። እንዲህ ሲል ጽፏል:- “የፍጥረት
ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ ይጠባበቃልና።” (ሮሜ 8:19)።
የጎልማሶች ሰንበት ትምህርት መምሪያ መጽሐፈ መዝሙረ ዳዊት
እንዴት ያለ አስደናቂ ተስፋ ነው!
ነገር ግን፣ የመጨረሻውን መዳን እና ከእግዚአብሔር ጋር መገናኘትን እየጠበቅን
ሳለ፣ “ፍጥረት ሁሉ እስከ አሁን ድረስ አብሮ በመቃተትና በምጥ መኖሩ” (ሮሜ 8፡22) ጌታ
አሁንም ከህዝቡ ጋር በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት አብሮ ይኖራል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በአዲስ ፍጥረት የሚደመደመውን የመዳን እቅድ
እንድንመሰክር ተጠርተናል (ሐዋ 1፡4-8)። ያ አዲስ ፍጥረት፣ የምንጠብቀው፣ እንደ
አድቬንቲስት ክርስቲያኖች የተስፋችን የመጨረሻ ፍጻሜ ነው፤ አድቬንቲስት፣ የሚል ስም
የምንጠብቀውን የተስፋ ሃሳብ ይዟል። እንጠብቃለን ግን መጠበቃችን በከንቱ እንዳልሆነ
እናውቃለን። የክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ፣ የመጀመሪያው ምጽአቱ እርግጠኛ እንደነበረ
ሁሉ፣ ለዳግም ምጽአቱም እርግጠኞች ነን።
አሁን ከእግዚአብሔር የምትጠብቃቸው አንዳንድ ነገሮች ምንድን ናቸው? በተለይ
የምንጸልየው ገና ካልተፈጸመ በእምነት እና በመተማመን መጠበቅን እንዴት እንማራለን?
መዝሙር 131ን ያንብቡ። ከአምላክ ጋር ስላለን ዝምድና ይህ መዝሙር ምን ያስተምረናል?
የእግዚአብሔር ሰዎች የሚኖሩት ታማኞችን በሚያስጨንቅ ዓለም ውስጥ ነው፣
ለሁሉም ማለት በሚቻል ልክ ዓለም በፈተና እና በችግር የተሞላ ነው። የእግዚአብሔር
ልጅ እንደሆነ እና ለህይወቱ በእግዚአብሔር ላይ እንዲደገፍ መደረጉ መዝሙረኛውን
በታደሰ እምነት እንዲጽናና እና ኩራቱ ምንም ዋጋ እንደሌለው እንዲናዘዝ አድርጎታል።
የትዕቢት አሳሳችነት ኩሩዎች በራሳቸው እንዲመኩና ከራሳቸው በላይ ማየት እንዳይችሉ
ያደርጋቸዋል። ስለዚህ ትዕቢተኞች እግዚአብሔር ከፍ ያለ ስለመሆኑ እውነታ ታውረዋል።
ከዚህ በተቃራኒ ጻድቃን ዓይኖቻቸውን ወደ እግዚአብሔር ያነሣሉ (መዝ 123፡
1፣ 2)። የእግዚአብሔርን ታላቅነት ማወቃቸው ትሑት እና ራስን ከፍ ከማድረግና
ከከንቱ ምኞት ነፃ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። መዝሙረኛው “ታላቅን ነገር” እና “ከፍታን
” እንደማይፈልግ ተናግሯል (መዝ 131፡1) ። እነዚህ አገላለጾች የእግዚአብሔርን ሥራዎች
በዓለም ላይ ከሰዎች መረዳት በላይ መሆናቸውን ይገልጻሉ። ዘመናዊ ሳይንስ ቢያንስ
ለአሁን እንኳን በሚያስደንቅ ሁኔታ ውስብስብ እና ከግንዛቤ በላይ ሊሆኑ እንደሚችሉ
አሳይቶናል። በእርግጥ፣ ስለ ግዑዙ አለም የበለጠ በተማርን ቁጥር በፊታችን የሚታዩ
ምስጢሮችም ይጨምራሉ የሚል አንድ ትልቅ ምፀት አለ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በመዝሙር 131፡2 ውስጥ “ከእናቱ ጋር እንዳለ ጡት
እንዳስተውት ልጅ” የሚለው ዘይቤአዊ አገላለጽ አንድ ሰው በእግዚአብሔር እቅፍ
ውስጥ በመሆን መረጋጋትን በማግኘቱ ዝም ማለቱን የሚያሳይ ኃይለኛ ምስል ነው።
ልጁ በሕጻንነት ዕድሜው ውስጥ በተለያየ ደረጃ ከእናቱ ጋር ያለውን የፍቅር ግንኙነት
ያመለክታል።
አምላክ የማይጨበጥ ምኞትንና የትዕቢት ጡትን ከመጥባት በማስጣል ጠንካራ
ምግብ ከመመገብ ጋር፣ ያውም “የላከኝን ፈቃድ አደርግ ዘንድ ሥራውንም እፈጽም ዘንድ”
(ዮሐ 4፡34 እና ዕብ 5፡12-14) ከሚለው ጋር ያስተዋውቀናል። በመዝ 131 ላይ የተገለጸው
የሕፃንን እምነት የመሰለ እምነት በህይወት ችግሮች የተፈተነ እና የጠራ፣ ለእግዚአብሔርና
ለቃሉ ታማኝ ሆኖ የተገኘና የበሰለ እምነት ነው።
መዝሙረኛው በመጨረሻ ትኩረት ያደረገው በእግዚአብሔር ሕዝብ ደህንነት ላይ
ነው። በመጨረሻ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ባገኘነው ልምምድ ቤተክርስቲያኑን እንድናጠነክር
ተጠርተናል። ማለትም፣ ስለ እግዚአብሔርን ታማኝነት እና ቸርነት በግል የተማርነውን፣
በማናቸውም ምክንያት በእምነታቸው በፈተና ላሉት ለሌሎች ማካፈል እንችላለን።
ስለ ክርስቶስ የምንመሰክረው ምስክርነት ብዙዎች ስለ እሱ ሊያውቁት በሚፈልጉበት
በቤተክርስቲያን ውስጥም እንኳን ሊሆን ይችላል።
“እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ
ሰማያት ከቶ አትገቡም” (ማቴ 18:3)። ኢየሱስ እዚህ ምን እያለን ነው ያለው? ይህ
ሀሳብ ምንን ያካትታል?
መዝሙር 126ን ያንብቡ። ለእግዚአብሔር ሕዝቦች ብርታትና ተስፋ የሚሰጣቸው ምንድን ነው? በዚህ አውድ ውስጥ ዛሬ በራሳችን ሕይወት ላይ ተግባራዊ ማድረግ የምንችለው የጎልማሶች ሰንበት ትምህርት መምሪያ መጽሐፈ መዝሙረ ዳዊት ምን እየተባለ ነው?
ባለፉት ዘመናት የጌታ ተአምራዊ ማዳን ለእግዚአብሔር ሕዝብ የማያልቅ
የመነሳሳት ምንጭ እና ለወደፊቱም የተስፋቸው ምንጭ ናቸው። ባለፈው ዘመናት ጌታ
ያደረገው ነጻ ማውጣት በጣም ትልቅ ከመሆኑ የተነሳ ህልም- ወደ-እውነተኛ ልምምድ
የተለወጠበት ተብሎ ሊገለጽ ይችላል (ኢሳ 29፡7፣ 8)። በመዝሙር 126 ቀድሞ ሕዝቡን
ከምርኮ ነፃ ስላወጣ (መዝ 126፡1) እግዚአብሔርን የሚያመሰግን ትውልድ አሁን በግዞት
ውስጥ እንዳለ ልብ ይሏል (መዝ 126፡4)።
ሆኖም፣ ያለፈው ደስታ እና እፎይታ በዝማሬዎች እንደገና ታድሰው አሁን ላለው
ልምምድ የተገቡ ናቸው። አዲሶቹ ትውልዶች የመጽሐፍ ቅዱስን ታሪክ በአይናቸው
ካዩት መካከል እንደ ተገኙ በመቁጠር ሕያው አድርገውታል። ስለዚህም ባለፉት ዘመናት
እግዚአብሔር ለህዝቡ ያደረገላቸውን ታላላቅ ስራዎች ለእነሱ ብቻ ሳይሆን ለእኛም
እንዳደረገልን በመቁጠር ሕያው እምነትን እንዲዳብር እናደርጋለን።
እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ያለፈው ትዝታ የአሁኑን ተስፋ ያድስልናል። “በደቡብ ያሉ
ወንዞች” (መዝ 126: 4) ምስል እግዚአብሔር ሕዝቡን ወክሎ በድንገት እና በኃይል
የሚያደርገውን ድርጊት የሚያሳይ ኃይለኛ ዘይቤ ነው። የይሁዳ ደቡባዊ ክፍል በረሃማ
አካባቢ ነበር። በዝናብ ወቅት ከሚጥለው ከባድ ዝናብ በኋላ ጅረቶቹ በድንገት ተፈጥረው
በጎርፍ ውሃ ይሞላሉ። የፊተኛውና የኋለኛው ዝናብ ለእርሻ ዓመቱ ስኬት ወሳኝ ሚና
ይጫወታሉ (ዘዳ 11፡14፣ ዘዳ 28፡12)። በተመሳሳይ፣ በእንባ የመዝራትና በደስታ የማጨድ
ምሳሌ (መዝ 126:5፣ 6) ከአስቸጋሪ ስጦታ ወደ አስደሳች ሕይወት የመምራት መለኮታዊ
ቃል ኪዳን ነው።
የመኸር ወቅት ማብቂያ የጥንት የዕብራውያን ተጓዦች የወቅቱን ፍሬዎች ወደ
ኢየሩሳሌም ወደ እግዚአብሔር ቤተመቅደስ የሚያመጡበት ጊዜ ነበር (ዘፀ 34: 22፣
26)። የመከሩ ሐሳብ በዚያን ዘመን ለነበሩት ሰዎች ኃይለኛ መንፈሳዊ ትምህርት ይሰጥ
ነበር። ማሳን፣ የፍራፍሬ እርሻን መንከባከብና ወይንን የመዝራትና የመንከባከብ ከባድ
ድካም በተትረፈረፈ መከር ደስታ እንደሚሸለም ሁሉ፣ አሁን ያሉት የእግዚአብሔር
ሕዝቦች ፈተናዎች በፍጻሜ ጊዜ የመዳንን ደስታ አክሊል ያስገኛሉ። የታላቁ መኸር ምሳሌ
እግዚአብሔር በክርስቶስ ዳግም ምጽዓት በምድር ላይ መንግሥቱን እንደገና እንደሚያድስ
ያሳያል (አሞጽ 9፡13-15፣ ማቴ 9፡37)። እዚህ ላይ ግን የመጠባበቅ ጭብጥ ይነሳል። እንደ
መኸር ሁሉ የድካማችንን ፍሬ እና ውጤት ለማየት መጠበቅ አለብን።
ጌታን በህይወታችሁ ወይም በሌሎች ህይወት ውስጥ ሲሰራ በግልፅ እና በማያሻማ ሁኔታ
ያያችሁበትን አንዳንድ ጊዜዎችን አሰላስሉ። አሁን እያጋጠመዎት ላለው ለማንኛውም ነገር
ከእነዚህ ልምምዶች እንዴት ተስፋ ማግኘት ይችላሉ?
መዝሙር 92ን ያንብቡ። በዚህ በሰንበት ቀን መዝሙር ውስጥ ጎላ ብለው የተገለጹት የሰንበት ሁለት ገጽታዎች የትኞቹ ናቸው?
ታላቅ ለሆኑ የእጁ ሥራዎች ለእግዚአብሔር ምስጋና ማቅረብ (መዝ 92፡
4፣ 5) እና ጻድቃንን ኤደንን በሚመስል ስዕል ማሳየት (መዝ 92፡12-14) ሰንበት
የሚያከብረው የመጀመሪያ ገጽታ ወደሆነው ፍጥረት በግልጽ ያመለክታሉ። መዝሙሩም
ጌታ የፍትህ አምላክ እንደመሆኑ በጠላቶቹ ላይ ስላደረገው ድል በማጉላት (መዝ 92፡
7-15) የሁለተኛውን የሰንበት ጭብጥ - ከክፋት የመቤዠትን ሥራ ያጠናክራል (ዘዳ 5፡
12-15)። ስለዚህ፣ መዝሙር 92 እግዚአብሔርን ስላለፈው ፍጥረቱ እና አሁን አለምን
ደግፎ ስለማቆየቱ ያወድሳል፣ እንዲሁም መለኮታዊ በሆነው ዘላለማዊ ሰላምና ሥርዓት
ወደሚገኘው የመጨረሻው ዘመን ተስፋ ይጠቁማል።
ሕዝቡ እግዚአብሔር “ልዑል” ስለሆነ የሰንበት ዕረፍትን ሊያጣጥሙት ይችላሉ (መዝ
92: 1)፤ እርሱ በከፍታዎች ላይ ያለው የላቀ ስለሆነ በጠላቶቹ ላይ ወደር የለሽ ድል ይቀዳጃል።
እርሱ ልዑል ቢሆንም፣ የሚጠሩትን ለማዳን ፈጥኖ ይወርዳል። የጌታ የፍጥረት
ሥራ እና በተለይም ፍጥረትን የመቤዥት ስራው ሰዎች እግዚአብሔርን እንዲያመልኩትና
እንዲወዱ ማነሳሳት አለባቸው። በወደቀ ፍጥረት ውስጥ በለተይ ያለ የመቤዠት ተስፋ
መኖር ፣ የሚያስደስት ነገር አይደለም። እናፈቅራለን፣ እንሰቃያለን፣ እንሞታለን - ያለ
ምንም ተስፋ እነዚህን ሁሉ እናደርጋለን። ስለዚህም ጌታን እንደ ፈጣሪያችን ብቻ ሳይሆን
እንደ አዳኛችንም እናመሰግነዋለን።
የጎልማሶች ሰንበት ትምህርት መምሪያ መጽሐፈ መዝሙረ ዳዊት
“አዲስ ዘይት” መዝሙረኛው እንደ ተቀደሰ አገልጋይ እግዚአብሔርን ለማገልገል
ያሳየውን የታደሰ አምልኮ ያሳያል (መዝ 92፡10)። በዘይት የመቀባት አገልግሎት እንደ
ካህናትና ነገሥታት ያሉ የተመረጡ ሰዎችን ለመቀደስ የሚፈጸም ተግባር ነው (ዘጸ 40፡
15፣ 1ሳሙ 10፡1)። ሆኖም መዝሙረኛው ቅባቱን ለመግለጽ ባላል የተባለውን ያልተለመደ
የዕብራይስጥ ቃል መረጠ፤ ይህም በተለምዶ የአምላክ አገልጋዮችን መቀባትን የማያሳይ
ሆኖ ከሌሎች የመሥዋዕቱ ክፍሎች ጋር ‘መቀላቀልን’ የሚያመለክት ነው (ዘጸ 29:2፤
ዘሌ2 :4፣ 5)። የመዝሙረኛው የባላል ልዩ አጠቃቀም መዝሙረኛው ራሱን እንደ
ህያው መስዋዕት አድርጎ ለጌታ ለማቅረብ እና ሙሉ ማንነቱን ለእግዚአብሔር ለመቀደስ
እንደሚፈልግ ያሳያል (ሮሜ 12፡1)።
ለሰንበት በተዘጋጀው መዝሙር ውስጥ ስለ መቀደስ ሀሳቦችን ማግኘት
አያስደንቅም። ምክንያቱም ሰንበት ጌታ ህዝቡን የሚቀድስ እንደሆነ የሚያሳይ ምልክት
ነውና (ዘጸ 31፡13)። የዘንባባ ዛፎች እና የሊባኖስ ዝግባዎች ምሳሌነት የእግዚአብሔር ሰዎች
በእምነት እና የእግዚአብሔርን ድንቅ ዓላማና ፍቅር በመረዳት በእውነተኛ አድናቆት
እያደጉ እንደሆነ ያሳያሉ። ሰንበት ጌታ ከሕዝቡ ጋር የገባው የዘላለም ኪዳን ምልክት ነው
(ሕዝ 20፡20)። ስለዚህ፣ የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ወሳኝ ነው ምክንያቱም
ጌታን በመተማመን የቃል ኪዳኑን ተስፋዎች እንዲፈጽም እንዲጠብቁ ኃይል ይሠጣቸዋል
(ዕብ 4፡1-10)።
መዝሙር 92ን እንደገና ያንብቡ። እዚያ ምን ዓይነት ታላቅ ተስፋ ቀርቦልናል? እኛስ
በአሁኑ ጊዜም ቢሆን በቃሉ ማጽናኛ ማግኘት የምንችለው እንዴት ነው?
መዝ 5:3፣ መዝ 30:5፣ መዝ 49:14፣ መዝ 59:16፣ መዝ 92:2፣ መዝ 119:147፣ 2 ጴጥ 1:19 እና ራእይ 22:16 ያንብቡ። እንደ መለኮታዊ የመቤዠት ጊዜ በምሳሌያዊ መንገድ የተገለጸው የትኛው ቀን ነው? ለምን?
በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ፣ ማለዳ በተለምዶ የእግዚአብሔር ቤዛነት የሚጠበቅበት
ጊዜ ነው። ማለዳ የእግዚአብሔርን ሞገስ ያሳያል፣ ይህም ረጅሙ የተስፋ መቁረጥ እና
የችግር ሌሊት ማብቂያ ነው (መዝ 130: 5፣ 6)። በመዝሙር 143፣ የእግዚአብሔር ማዳን
አሁን ያለውን የሞት ጨለማ (መዝ 143፡3) ወደ አዲስ ጠዋት ብርሃን (መዝ 143፡8) እና
ጕድጓድ ውስጥ መሆንን (መዝ 143፡7) ወደ “የጽድቅ ምድር” መኖሪያነት ይለውጠዋል።
(መዝ 143፡10)።
ማርቆስ 16፡1-8 ያንብቡ። በጠዋቱ ስለተከሰተው ነገር እዚህ ጋ ተነግሯል፣ እና ይህ ለእኛ
በጣም አስፈላጊ የሆነው ለምንድነው?
በጠዋት የተከሰተው የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በስሙ ለሚያምኑ ሁሉ
ለዘለአለማዊው የእግዚአብሔር የማዳን ንጋት መንገድ ከፍቷል። የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት
በመዝሙር 30፡5 ላይ ያለውን የተስፋ ቃል በሙሉ ኃይላቸው አጣጥመዋል፡- “ልቅሶ ማታ
ይሆናል ደስታ ግን በጠዋት ይመጣል” በማለት ከሞት የተነሳውን ጌታ አግኝተውታል።
ልቅሶአችን ወደ ደስታ የሚለወጠው በእግዚአብሔር ሞገስ እና ምክንያት አልባ በሆነው
ፍቅር ብቻ ነው (መዝ 30፡5፣ 7)።
የንጋት ኮከብ አዲስ ቀን መወለድን እንደሚያውጅ፣ እምነትም በእግዚአብሔር
ልጆች ውስጥ ያለውን የዘላለም ሕይወት አዲስ እውነታ ያበስራል (2ጴጥ 1፡19)። ኢየሱስ
ብሩህ የንጋት ኮከብ ተብሎ ተጠርቷል (ራዕ. 22፡16)፣ እርሱም ሌሊት፣ ክፋትና ሞት
የማይኖርበትን የመንግሥቱን መመሥረት በጉጉት የምንጠብቀው (ራዕ 21፡1-8፣ 25)
ነው። በመጨረሻ፣ ከምንም ነገር በላይ፣ ጌታን ስለመጠበቅ ስንናገር የነበረው ይህ ነው።
በእርግጠኝነት ይህን መጠበቅ ዋጋ አለው።
“በተከፈተው የዮሴፍ መቃብር ላይ፣ ክርስቶስ በድል አድራጊነት ‘ትንሣኤና
ሕይወት እኔ ነኝ’ ብሎ ተናግሮ ነበር። እነዚህ ቃላት ሊነገሩ የሚችሉት በመለኮት ብቻ
ነው። ፍጥረታት ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድና ኃይል ይኖራሉ። ከሊቀ ሱራፌል እስከ
ትሑት ሕያው ፍጡር ድረስ ሁሉም የሕይወት ምንጭ በሆነው በእግዚአብሔር ሕይወት
ላይ ጥገኛ ናቸው። ነፍሴን አሳልፌ ልሰጥ ደግሞም ልነሣት ሥልጣን አለኝ ሊል የሚችለው
ከእግዚአብሔር ጋር አንድ የሆነ ብቻ ነው። በአምላክነቱ፣ ክርስቶስ የሞትን እስራት
የመበጣጠስ ኃይል ነበረው።”—Ellen G. White፣ The Desire of Ages፣ ገጽ. 785.
ሞት ስንወለድ በሴሎቻችን ውስጥ ተቀርጿል ተብሏል። ይህ እውነት ቢሆንም፣ ቢያንስ
ለእኛ ለወደቅን ፍጥረታት፣ የኢየሱስ ትንሣኤ ስለ ሞት ጊዜያዊነት ምን ቃል ገብቷል?
የጎልማሶች ሰንበት ትምህርት መምሪያ መጽሐፈ መዝሙረ ዳዊት
ጊዜያዊ ሞት ለእኛ ምን ያህል እንደሆነ ፈጽሞ መዘንጋት የሌለብን ለምንድን ነው?
Read Ellen G. White, “Growing Up Into Christ,” pp. 67–
75, in Steps to Christ ያንብቡ።
መዝሙራት ጌታን እንድንጠብቅ አጥብቀው ይማጸናሉ። “ለእግዚአብሔር ተገዛ፥
ተስፋም አድርገው” (መዝ 37:7)። መጠበቅ ሸክም ሲሆንብን፣ እርግጠኛ ያለመሆንና
ብቸኝነት ሲገጥመን፣ ኢየሱስ ወደ ሰማይ ባረገበት ቀን ደቀ መዛሙርቱ የገጠማቸውን
ማስታወስ አለብን (ሐዋ 1፡4-11)። እነሱም ወደ ኋላ ቀርተው ወደ ፊት ባልታወቀ ቀን
ተመልሶ እስኪመጣ ድረስ እንዲጠብቁት ኢየሱስ በዓይናቸው እያዩት ወደ ሰማይ ተወሰደ።
በዚያ ቀን ከደቀ መዛሙርቱ የበለጠ የአምላክን በረከት ለማግኘት በከፍተኛ ጉጉት ያሳለፈ
ማን ይኖራል? በእርግጥ “ጌታ ሆይ፣ አሁን ከአንተ ጋር ውሰደን” ብለው መናፈቃቸው
አይቀርም። ሆኖም፣ የአብን የተስፋ ቃልና የኢየሱስን መምጣት እንዲጠብቁ ታዝዘዋል።
ደቀ መዛሙርቱ በተስፋ መቁረጥና በብስጭት የተሞሉ መስሎ ቢታየን እንገረም ነበር።
ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ እና ኢየሱስ የነገራቸውን አደረጉ - የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ
መውረድ ጠብቀው ከዚያም በኃይል ወንጌልን ለአለም ሰብከዋል (ሐዋ 1፡12-14፣ ሐዋ 2)።
ጌታችን እርሱን እንድንጠብቅ ያዘዘን ትእዛዝ እርሱ በእኛ ውስጥ በመንፈስ
ቅዱስ በኩል ሥራውን ካልሠራ በቀር የማይቻል ነው። ደካማ በሆነው እኛነታችን ላይ
መጠበቅ የሚፈጥረውን ጫና ምንም ያህል ሰብአዊ ግለት መቋቋም አይችልም። ውጥረቱን
መሸከም የሚችለው አንድ ነገር ብቻ ነው፣ እርሱም በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ መኖር፣
እሱም ከእርሱ ጋር ያለን ግላዊ ግንኙነት ነው። “እንግዲያውስ ክርስቶስ በልባችን ውስጥ
የሚኖር ከሆነ፣ እርሱ በእኛ ውስጥ ‘ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም ይሠራል።’
ፊልጵ 2፡13። እርሱ እንደሰራው እንሰራለን፤ ያን ተመሳሳይ መንፈስ እንገልጣለን። እርሱን
በመውደድና በእርሱ ውስጥ በመኖራችን ‘በሁሉም ነገር ወደ እርሱ ራስ ወደሆነው ወደ
ክርስቶስ እናድጋለን።’ ኤፌ 4:15።”—Ellen G. White፣ Steps to Christ፣ p. 75. ጌታን
ስንጠብቅ፣ በመዝሙራት ውስጥ የተገለጸውን ሰላም እና እርካታን እናገኛለን። ጸሎታችን
እና መዝሙራችን የእግዚአብሔር ልብ እና ልባችን በየቀኑ የሚገናኙበት ይሆናል።
1. መጠበቅ በመንፈሳዊ ሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ለምንድን ነው?
መጠበቅ በመንፈሳዊ ሕይወታችን ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ለምንድን ነው?
የአንዳንድ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የእምነት ጀግኖችን የመጠበቅ ልምድ ተወያዩ። መጠበቅ
እምነታቸውን ያጠናከረው እንዴት ነው? (ሮሜ 4:19-22፣ ዕብራውያን 11)
2. የመጠበቃችን መጨረሻው ምንድን ነው? (መዝ 37፡34–40):: ሁሉም ነገሮች
የመጠበቃችን መጨረሻው ምንድን ነው? (መዝ 37፡34–40):: ሁሉም ነገሮች
በመጨረሻ ሲፈቱ ምን ቃል ተገብቶልናል? በዚህ ሕይወት ውስጥ ለረጅም ጊዜ
ስለጠፋው ፍትህ በእነዚህ ጽሑፎች ውስጥ ምን ተስፋ እናገኛለን?
3. ሙታንን በተመለከተና በራስዎ ተሞክሮ (መክ 9:5) ኢየሱስን መጠባበቅ የጀመሩት
ሙታንን በተመለከተና በራስዎ ተሞክሮ (መክ 9:5) ኢየሱስን መጠባበቅ የጀመሩት
ለምንድን ነው? ከመልሱ ምን ተስፋ ልናገኝ እንችላለን?
ማሳሰቢያ
ድርጅቱ